የባለስልጣኑ ስልጣንና ተግባራት በዝርዝር


  • ድርጅቶችን መመዝገብ፣መደገፍ፣ስራቸውን ማሳለጥና ማስተባበር፤
  • ድርጅቶች ስራቸውን በህግ አግባብ ማከናወናቸውን ለማረጋገጥ አስፈላጊውን ክትትልና ቁጥጥር ማድረግ፤
  • የድርጅቶችን ዓመታዊ የስራና የገንዘብ እንቅስቃሴ ሪፖርት በዚህ ሕግ በተወሰነው መሰረት መመርመር፤
  • ድርጅቶች ግልጽነትና ተጠያቂነትን የሚያረጋግጥ የውስጥ አስተዳድር እና የራስ አስተዳድር ስርዓት እንዲኖራቸው አስፈላጊውን ድጋፍ መስጠትና ተፈጻሚነቱን መከታተል፤
  • ከሚመለከተቸው የክልል መንግስታት አካላት ጋር በመተባበር በአገሪቱ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶችን ቁጥር፣ተሰማሩባቸውን እና የአባሎቻቸውን ብዛት እና መሰል መረጃዎችን የሚይዝ የመረጃ ማዕከል ማቋቋም እንዲሁም  እነዚህን መረጃዎች መተንተን እና በጋዜጣና በድረ-ገጽ አሳትሞ ማሰራጨት፤
  • ከፌደራልና ከክልል የመንግስት አካላት እንዲሁም ከድርጅቶች ጋር ቋሚ የምክክር መድረኮችን ማዘጋጀት፤
  • ኃላፊነቱን ለመወጣት ከዘርፍ አስተዳዳሪዎች ጋር በትብብር መስራት፤
  • ድርጅቶች መንግስት በሚያወጣቸው ፖሊሲዎች ሕጎች የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ማበረታታት፤
  • ድርጅቶች በአገሪቱ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ፣ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ እና የልማት አንቅስቃሴ ያላቸውን ሚና አስመልክቶ ተገቢውን ጥናት ማካሄድና መንግስት ማማከር፤
  • ድርጅቶች የሚያከናውኗቸውን የልማት ስራዎች መንግስት ከሚያወጣቸው የልማት ዕቅዶች ጋር የተጣጣሙ እነዲሆኑ የሚያግዙ የፖሊሲ መመሪያዎችን ማዘጋጀት፤
  • አግባብነት ባላቸው ሕጎች ስለሰነዶች ማረጋገጥና ምዝገባ የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ የድርጅቶችን መተዳደሪያ ደንቦችና ማሻሻያዎቻቸውን ማረጋገጥና መመዝገብ፤
  • የአገልግሎት ክፍያዎችን በዚህ አዋጅ መሰረት በሚወጣ ደንብ መሰብሰብ፤
  • የንብረት ባለቤት መሆን፣ውል መዋዋል፣በራሱ ስም መክሰስ እና መከሰስ፤
  • አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው በዚህ አዋጅ ተሰጡትን ስልጣንና ተግባራት ለሌሎች አካላት በውክልና መስጠት፤
  • አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው በየትኛውም የአገሪቱ ክፍል ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቶችን መክፍት፤
  • በዘርፉ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረትን ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከል የሚያስችሉ ስራዎችን ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ጋር በትብብር መስራት፤
  • ድርጅቶች ሲፈርሱ በሒሳብ አጣሪነት የሚያገለግሉ ባለሙያዎችን ዝርዝር ማዘጋጀትና ስራዎችን ባግባቡ መከናወናቸውን መቆጣጠር፤
  • በአዋጅ የተቋቋመውን የሲቪል ማህበረሰብ ፈንድ ማስተዳደር፤
  • የበጎ ፍቃደኝነትን ባህልና እንቅስቀቃሴ ማበረታታት፤የበጎ ፍቃደኝነት በተመለከተ የስርጸት ስራ መስራት፤
  • ዓላማውን ለማስፈጸም የሚያስፈልጉ ሌሎች ተግባራትን ማከናወን፤